Tuesday, August 25, 2015

ፂምም የለዎት?

 በሁሰን ከድር

እኚህ ሰውዬ የፌዴራል እስልምና ጉዳዮች ፕሬዚዳንት እንደሆኑ ዛሬ በወጣ መጽሔት ላይ አየሁ፡፡ ያለዛሬም አይቻቸው አላውቅም፡፡እማውቅበት እድሉም የለም፡፡ በኦርቶዶክስ ክርስትና ፓትርያርኩ ፂማቸው ተንዠርግጎ ሲታይ የሃይማኖት አባትነታቸው ጎልቶ ይታያል፡፡ የካቶሊኩም ቄስ ፂም ያላቸው ይመስለኛል፡፡ የአይሁድም ራባዮች ፂማቸው ጎልቶ ይታያል፡፡ ሰማያዊ ሃይማኖት ተከታይና መሪዎች ፂም አልባ ሆነው አይቼ አላውቅም፡፡
የሃይማኖት መሪዎች በሃይማኖት ትምህርት የላቁ ሆነው መገኘታቸው ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ዘመናዊ ትምህርት ካከሉበት የተሻለ ነው፡፡ የለ ጠልቄ አልግባ.... የመጅሊሱ መሪ ፂም አልባ የተፈጥሮ ይሆን? የተፈጥሮ ከሆነ ምንም አይደል ከሕዝብ ጋር የሚያደርጉትን መስተጋብር አይተን ከሿሚያቸው ጋር በማንጸር ሃሳባቸውን እንገመግማለን፡፡
ግን ፂማቸውን ሼቭ አስደርገው ከሆነ ቢሮ የሚገቡት የተመደቡበትን መስሪያ ቤት ሳያውቁት ቀርተው ይሆን?
በየጊዜው መንግሥት የሚሾምልን ጓዶች መቼም አንዳንድ ነገር አያጣቸውም፡፡ ህምም...
አላህ ያሳያችሁ መሪዎቻችንን እኛ ጭቁን ሕዝቦች ብንመርጥ ኖሮ .....

No comments:

Post a Comment